Tuesday, September 29, 2015


እፍ በላት ጌታዬ


ወርቁ በላቸው
የክረምቱ ብርድ እንደዛሬው አልነበረም፡፡ ገና ሰኔ ሲያስገመግም የሰፈራችን ሰወች መሸበር ይይዛሉ፡፡ በጋራ የተከበበችውን መንደራችንን ልብና ሆዷን እንየቦረቦሩ፣ እንደ አንበሳ እያጋሱ፣ ቋጥኝና ዛፉን እያንከባለሉ የሚጋልቡ ወንዞች አሏት፡፡ ስለዚህ ሕፃናት ልጆች ያሏቸው ወላጆች ልጆቻቸው ወደ ወንዝ እንዳይወርዱ ቀድመው ያስጠነቅቃሉ፡፡ አሮጊትና ሽማግሌዎችም ጨርቅ ለማጠብ ወይም ለሌላጉዳይ ወደ ወንዞቹ ከመሄድ ይቆጠባሉ፡፡ 

አዲስ አበባ እንደዛሬ ወንዞቿ ለአይን አስቀይሞ ጠረናቸው ከሩቅ ሳይገፋተር፣ የብዙዎቻችን መታጠቢያ፣ መዋኛና አልፎ ተርፎም መጠጥም ነበሩ፡፡ በተለይ የቀበና ገባሮች፣ ከላይ ጥንስስ ጀምሮ እስከ አባንጉሴ ድረስ የነበራቸው ገፅታ ልዩ ነበር፡፡ ሕዝብ እንዳሁኑ በብዛት አልሰፈረም፣ ቆሻሻም እንደተራራ አይቆለልም ነበረ፡፡
ክረምት ማለት ያኔ ሰማይ ተቀዶ ውሃ የሚንዠረዠርበት ወቅት ነበር፡፡ ብርዱ አጥንትን ዘልቆ መቅኒን ይነካል፡፡  በተለይ ደጋማ በሆኑ የአዲስ አበባ ክፍሎች፣ ደመናው መሬት ወርዶ እንደጢስ ሲትጎለጎል ማየት ብርቅ አልነበረም፡፡ ነዋሪው በዚህ ወቅት ጋቢና ደበሎውን ለብሶ እየቀፈፈው ነው ጉዳዩን የሚተኩሰው፡፡ ልጆች ደግሞ ጥሬያችንን እየቃምን ሰማዩን እንቃኛለን፡፡ ከአሁን አሁን ፀሀይ ወጣች እያልን፡፡
ከመንደራችን ፊት ለፊት ባለች ጠባብ መንገድ ላይ ሆነን ፀሀይን እንለምናታለን፣ ፀሀዬ ውጪ ውጪ ዳመና ተገልበጪ፣ ፀሀዬ ውጪ ውጨ ዳመና ለጎመኔ ለኔ ለኔ›››› እኛ የታች ሰፈር ልጆች እናቀልጠዋለን፡፡ የላይ ሰፈር ልጆች ደግሞ ከመንደራችን በስተ ምስራቅ አቅጣጫ ባለ ኮረብታ ላይ ይደረደራሉ፡፡ ቁልቁል እኛን እያዩ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው መጮህ ይጀምራሉ፡፡ እንለምናታለን፣ ፀሀዬ ውጪ ውጪ ዳመና ተገልበጪ፣ ፀሀዬ መውጪ ውጨ ዳመና ለጎመኔ ለኔ ለኔ›››› አሁን ዳኛ የሌለው ውድድር ተጀመረ ማለት ነው፡፡ በቃ መንደሯ በእንድ እግሯ ትቆማለች፡፡ አንዳጋጣሚ ይሁን ወይ እኛን ሰምታ ፀሐዩዋ ትወጣለች፡፡ አሁን ደግሞ ሌላ ንትርክ ይጀመታል፡፡ የኛ መንደሮቹ ወጣች፣ ወጣች… ስንል የላይኛዎቹ ደግሞ መንጫጫት ይጀምራሉ፡፡ ነገሩ ምን መሰላችሁ፣ እኛ የምናስበው የኛ ድምፅ ከፍተኛ ስለሆነ ተሰማ ስንል፤ እነሱ ደግሞ የለም እኛ ኮረብታ ላይ ስለሆንን የተሰማው የኛ ነው ባይ ነበሩ፡፡ ሁላችንም ግን አንድ ነገር እርግጠኞች ነበርን፣ ፀሀይ በክረምት ትሰማለች፡፡ እኛ ሕፃናት የመንደራችን ብርድ ሲያንሰፈስፈን፣ ፀሃዬን እንማፀናታለን፡፡ እሷም ትታዘዘናለች፡፡
ያኔ የሚገርመኝ ነገር ግን የአያቴ ተማጽኖ ነበር፡፡ እንደ ጥጥ የነጣ ፀጉሯን ዳበስ ዳበስ እያረገች ከግቢው ባለ አንድ ትልቅ ቆርቆሮ በር ስር አጎዛ መሳይ ነገር ዘርግታ ትቀመጣለች፡፡ አንዳንዴ የሚደንቀኝ ጉዳይ ምንም ፀሀይ ሳይኖርም እጆቿን እንደ ባርኔጣ ግንባሯ ላይ ጋረድ አድርጋ ሰማዩን ቀና ብላ ፀሀዩዋን ትፈላልጋለች፡፡ ሰውነቷ የያዘው ሙቀት እያለቀና ብርዱ እያየለ ሲመጣ እትትተት…. እያለች አምላኳን መማፀን ትጀምራለች፡፡ እፍ በላት ጌታዬ …እፍ በላት ….. እየደጋገመች፡፡ እንግዲህ ለአያቴ ፀሀይ ማለት የእግዜር ምድጃ አይነት ነገር ናት፡፡ እግዜር ደግሞ መቆስቆሻ ይዞ የሚያነዳት ነዋ፡፡ ግን የሚገርመው እሷ እፍ በላት ጌታዬ ስትለው ደመና እንደ አመድ የወረሳትን ፀሀይ ግልጥ ያደርግና፣   ወከክ አድርጎ ያነድላታል፡፡ እሰይ ጌታዬ እሰይ …. እያለች ደግሞ ማመሰጋገን ትጀምራለች፡፡ አሁን ደግሞ የሚገርመኝ ለምን እፍ በያት እመቤቴ አለማለቷ ነው፡፡ ፀሀይን እንደ ማዕድ-ቤቷ እሳት ስትቆጥር ጌታ ወንድ ስለሆነ እዚያ ምን ያደርጋል አለማለቷ፡፡

Tuesday, September 15, 2015

Rhythm of seasons !


A beautiful beauty that quenches thirst of heart
Which fills sprit, with joy head to toe
A gift of gift, that no one can present
A treasure, dug only under, the yard of the creator
A pile of time
Packed in seasons
True and natural rhythm
Spiraling and whirling life’s dance
Beats of eternal drum
 Oh! Creator thy plans
Never collapse. 

Kiramt (rainy season) showers on sea and land
Wet  every soul, unlock door of the seed
All in the heart of earth starts to breed
Mountains adorn, with blanket of green
Valleys with run offs, and falls
Rivers fills to their brim, gush to sea leaves
Dance, with beats  of the drum, and charming rhythm


Oh! Creator Kiramt did duty
 Pass on a relay of beauty
And the skies turn clear, the sun shines free
Yellows  the grasses, shrubs and tree.
Plants comes to flower, a yellow army
Adey Abeba conquers hills and valley

Wereha Tsegie (flowering season) comes with promises
Assure that all sown will come to seed
All thrown becomes a yield.
Oh! Creator thy task gets old never
Always fresh always glitter.

How tiny are years before you
A priceless belonging
That you confer on master and servant
How cheap are days before you
A cherished good

But for you and to all a free grant. 

Worku Belachew Sept. 2015

Wednesday, September 2, 2015